ጥራት ያለው የቴክኒክ ሙያ ስልጠና በመስጠት ብቃቱ የተረጋገጠ በዝቅተኛና መካከለኛ ደረጃ የሰው ሀይልና ቴክኖሎጂ ማቅረብ፣ የጥቃቅና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች በስፋት እንዲቋቋሙ በማድረግ ሰፊ የሥራ ዕድል መፍጠር፣ ለኢንተርፕራይዞቹ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት በመስጠት በገበያ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ በማድረግ ለኢንዱስትሪያሊስቶች መሰረትና መፍለቂያ እንዲሆኑ ማስቻል፡፡
ለኢንዱስትሪ ልማት አሰተማማኝና ሰፊ መሰረት ያለው በመካከለኛ ደረጃ የሰለጠነ የሰው ኃይልና ልማታዊ ኢንተርፕራይዞች ተስፋፍተው በ2030 መካከለኛ ገቢ ያለው ህብረተሰብ ተፈጥሮ ማየት
በሚከተሉት እሴቶችና እምነቶች ላይ አተኩረን እንሰራለን፡-
o ደንበኞችን በቅንነትና በታማኝነት እናገለግላለን፣
o በቡድን የመስራትና ውጤታማ መሆንን ባህላችን እናደርጋለን፣
o አዳዲስ እውቀቶችንና ክህሎቶችን የመማማር ባህልን እናዳብራለን፣
o ኪራይ ሰብሳቢነትን በመታገል በመልካም ሥነ ምግባር የታነፁ ሠራተኞች እንሆናለን፣
በጥራትና ተወዳዳሪነት እናምናለን፣